መስከረም 6 ፣ 2014

ሀሰት፡ ምስሉ በቅርቡ በመቀሌ ከተማ የተደረገን የከባድ መሳሪያ ጥቃት አያሳይም

HAQCHECK

ምስሉ በቅርቡ በከተማዋ የተከሰተ ሁኔታን የሚያሳይ ባለመሆኑ ሀሰት ነው።

Avatar: Rehobot Ayalew
ርሆቦት አያሌው

Rehobot is a lead fact-checker at HaqCheck. She is a trainer and a professional who works in fact-checking and media literacy.

ኪሩቤል ተስፋዬ

Kirubel works as a fact-checker at Addis Zeybe for HaqCheck. He is interested in learning and expanding his writing and journalistic skills.

ሀሰት፡ ምስሉ በቅርቡ በመቀሌ ከተማ የተደረገን የከባድ መሳሪያ ጥቃት አያሳይም

ጳጉሜ 3 2013 ዓ.ም ከ11 ሺህ በላይ ተከታይ ያለው የፌስቡክ ገጽ  በከባድ መሳሪያ የታገዘ የተኩስ ድምጽ በመቀሌ ከተማ ተሰምቷል በማለት አንድ ምስል አጋርቷል።

በተጨማሪም ልጥፉ “ከመቀሌ 49 ኪ.ሜ  ርቃ በአፋር ክልል በምትገኘው እና  አብላ ተብላ የምትጠራው ከተማ ድረስ የተኩስ ድምጽ ይሰማ እንደነበረ ጽፏል”።

ይሁን እንጂ ምስሉ በቅርቡ በከተማዋ የተከሰተ ሁኔታን የሚያሳይ ባለመሆኑ ሀሰት ነው።

በጥቅምት 2013 ዓ.ም ሕውሃት በሰሜን ዕዝ የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት ላይ የፈጸመውን ጥቃት ተከትሎ በኢትዮጵያ ፌደራል መንግስት እና ሕውሃት ጦርነት መጀመሩ ይታወሳል። ጦርነቱ ከተጀመረ ከሶስት ሳምንታት በኋላ የፌደራሉ መንግስት መቀሌን ጨምሮ አብዛኛውን የክልሉን ከተሞች ተቆጣጥሯል። ነገር ግን ስምንት ወራትን ከፈጀው ጦርነት በኋላ የፌደራሉ መንግስት የተናጥል የተኩስ አቁም ስምምነትን በማወጅ በክልሉ የነበሩትን የመከላከያ እና የክልል ልዩ ሃይሎችን ከክልሉ እና ከአካባቢው አስውጥቷል

በ ሰኔ 21 2013 ዓ.ም የፌደራል መንግስቱ የተናጥል የተኩስ አቁሙን ስምምነት  ይፋ አድርጎ ከክልሉ ለቆ መውጣት ከጀመረበት ጊዜ አንስቶ የሕውሃት ሃይሎች የክልሉ ዋና ከተማ የሆነችውን መቀሌን መቆጣጠር ችለዋል። በአሁኑ ሰዓት ግጭቱ ወደ አማራ እና አፋር ክልል አጎራባች አካባቢዎች ተስፋፍቷል። 

ይህ በእንዲህ እንዳለ የፌስቡክ ልጥፉ ከባድ መሳሪያ ጥቃት የሚመስል ፍንዳታን የሚያሳይ ምስልን አጋርቷል።

ሆኖም ሪቨርስ ኢሜጅ የተባለው የተገላቢጦሽ የምስል ፍለጋ እንደሚያሳየው ምስሉ ለመጀመሪያ ጊዜ የተለቀቀው ሕዳር 7 2013 ዓ.ም በቪኦኤ አማርኛ ድህረ-ገጽ ላይ ነው። ምስሉም የተለቀቀው ድህረ-ገጹ በትግራይ ወቅታዊ ሁኔታ ላይ ባወጣው ዘገባ ላይ ነበር። ዘገባውም ባሰፈረው ጽሁፍ በመቀሌ ከተማ በደረሰ የአየር ጥቃት አንድ ሰው ላይ ጉዳት መድረሱንና የመኖሪያ ቤቶች መፍረሳቸውን አመላክቷል።

ስለዚህ በፌስቡክ ልጥፉ የተመለከተው ምስል በቅርቡ በከተማዋ መቀሌ ደረሰ የተባለውን የተኩስ ድምጽ እና በከባድ መሳሪያ የታገዘ ጥቃትን የሚያሳይ ስላልሆነ ምስሉ ሃሰት ነው።   

አስተያየት