ከአዲስ አበባ 91.9 ኪሜ ርቀት ላይ ያለች ስምጥ ሸለቆ ውስጥ የምትገኝ ከተማ ነች። ምስራቅ ኢትዮጵያን ከመዲናይቱ ጋር የምታገናኝ የንግድ እና የትራንስፖርት ከተማ ስትሆን የኮንፈረንስ ቱሪዝም መዳረሻ ነች፡፡
በየቀኑ እስከ 100 የሚደርሱ አህያዎች በኢትዮጵያ እንደሚታረዱ የተገለፀ ሲሆን በዚህ ከቀጠለ ሀገሪቱን አህያ ከማሳጣት ባለፈ የስራ ጫናዎችን በመፍጠር ማህበራዊ ቀውስም ሊያስከትል ይችላል
የጥምቀት በዓል በተለየ እና በሌሎች የኢትዮጵያ ክፍሎች ያልተለመደ በሆነ ሁኔታ በድምቀት የሚከበርበት 'ሃሮ-ደንበል' ዘንድሮ እስከ 100 ሺህ ታዳሚዎች ይገኙበታል ተብሎ ይጠበቃል
በኢትዮጵያ ውስጥ የሚገኙ ባትሪዎች ከውጭ የሚመጡ ሲሆኑ በሀገር ውስጥ ጠግኖ ወደ ምርት የሚመልሰው ብቸኛው አዋሽ ባትሪ በአሁኑ ወቅት በስራ ላይ አይገኝም።
በአዳማ ሆፒታል የካንሰር ማዕከል የአዲስ ዘይቤ ከፍተኛ የሆነ የመገልገያ መሳሪያዎች፣ የአስፈላጊ ግብዓቶች እንዲሁም የመገልገያ ግንባታዎች ችግር ተመልክቷል
ህገ ወጥ የነዳጅ ሽያጭ እና ክምችት መበራከቱ ስጋት ፈጥሯል። አሽከርካሪዎች በነዳጅ እጦት ሳቢያ ከህገ ወጥ ነጋዴዎች በእጥፍ መግዛት እና ህገ ወጥ ነዳጅ ክምችት ባለባቸው አካባቢዎች የአደጋዎች መከሰት ዋነኛ ችግር ሆነዋል።
ሰዓሊ አለ ፈለገሰላም የማርያም ቤተክርስትያንን ሥዕል ለመሳል አዳማ ከመጡ በኋላ በ 2000 ዓ.ም ወደ አዲስ አበባ እስኪመለሱ ድረስ እዚያው መሬት ገዝተውና ቤት ሰርተው ለአመታት ኖረዋል
ድምጻዊ አህመድ ተሾመ (ዲንቢ) “የትዝታው ፈረስ” በተሰኘው ሙዚቃው ውስጥ እንዲህ ሲል አዚሟል፥ “የሳር ተራው ሲሳይ ያስመሸኝ ካራዳ፣ የድሃ እራት ንፍሮ የብርቅዬ ጓዳ”
በአስገራሚ የመተጣጠፍ ችሎታው በዓለም የድንቃ ድንቅ መዝገብ (Guinness World Records) የራሱንና የኢትዮጵያን ስም ማስጠራት የቻለው ኪሮስ ሃድጉ የሰርከስ አዳማ ፍሬ ነው
የፌዴራሉም ሆነ በኦሮሚያ ህገ-መንግስት ማንኛውም የፍርድ ቤት ዳኛ እጅ ከፍንጅ ካልሆነ በቀር ያለመከሰስ መብቱ በህጋዊ መንገድ ሳይነሳ መከሰስ እንደማይችል ይደነግጋል
በአራት ዓመታት ውስጥ ለመጀመሪያ ጊዜ የተደረገው የዋጋ ጭማሪ ከ57 በመቶ እስከ 90 በመቶ የሚደርስ ጭማሪ አለው።