ደሴ በሰሜን መሀል ኢትዮጵያ የምትገኝ ከተማ ናት። በአማራ ክልል ደቡብ ወሎ ዞን ውስጥ የምትገኘው ደሴ ከመዲናይቱ አዲስ አበባ በስተሰሜን 400 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ትገኛለች። በ30 ቀጠናዎች ውስጥ ከ200,000 በላይ ሰዎች አሏት።
በደሴ ከተማ ውስጥ የሚገኙ 88 ኢንተርፕራይዞች የወሰዱትን የተዘዋዋሪ ፈንድ ብድር መክፈል አልቻሉም።
የቤተመንግስቱ አጥር በወቅቱ ባለመታደሱና የውስጥ ቅርሱም ጥበቃ ስለማይደረግለት ለከፋ ጉዳትና ጥፋት እየተዳረገ ይገኛል።
የመጀመሪያውን ዙር ኘሮጀክት በጨረታ ያሸነፈው ኮንትራክተር በ2007 ዓ.ም. ግንባታውን ጀምሮ በግንባታ ቁሳቁሶች ዋጋ መናር ምክንያት በታቀደው ጊዜ አጠናቆ ማስረከብ አልቻለም
ከሚቀርቡት ምክንያቶች መካከል መዝገብ ቤት ታሽጓል፣ ማህተም በወረራው ወቅት ስለተዘረፈ እስኪቀረጽ ጠብቁ፣ ፋይል በማጣራት ላይ ስለሆንን ትንሽ ጠብቁ፣ የሚሉ እንደሚገኙበት ሰምተናል።
የአራቱ ሐይማኖቶች ተወካዮች በጋራ በሰጡት መግለጫ ትምህርት ሚኒስቴር የከተማዋን ነባራዊ ሁኔታ ከግምት ውስጥ ሳያስገባ ያስቀመጠው የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ውጤት ኢ-ፍትሐዊ ነው።
አርሶ አደሮቹ በማሳቸው ላይ የሚገኘውን ተክል የረዥም ጊዜ ጉዳት ከተረዱ በኋላ ማሳቸውን ጠቃሚ ወደ ሆኑ የፍራፍሬ ምርቶች እየቀየሩ እንደሚገኙ ከአቶ ገብሩ ተረድተናል።
ተፈናቃዮቹ ወደ አማራ ክልል ለመፈናቀል ያስገደዳቸውን ምክንያት ሲጠየቁ የሰላም ማጣት፣ የምርት እጥረት፣ መንግሥት አልባነት፣ ስርአተ-አልበኝነት የአደጋ ስጋትና ረሀብ በማስከተላቸው እንደሆነ መግለጻቸውን ኃላፊው አንስተዋል።
የ”አበጋር” የሽምግልና ስርአት በየአካባቢው ከሚፈጠረው የግለሰቦች ጸብ አንስቶ የአፋር እና ኦሮሚያ ክልሎች ነዋሪ ድንበርተኞች መካከል የሚፈጠርን አለመግባባት ይፈቱበታል።
ጦርነቱ ከፍ ያለ ማኅበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ጉዳት ካስከተለባቸው የኢትዮጵያ ከተሞች መካከል ደሴ አንደኛዋ ምናልባትም ዋነኛዋ ተብላ ልትጠቀስ ትችላለች።
ቤተ-መጻሕፍቱ በመደበኛ ትምህርት ላይ የሚገኙ ተማሪዎችን ከመርዳት ባሻገር ወንጀል እንዲቀንስ፣ የሱስ ተገዢነት እንዳይበራከት በማድረግ አማራጭ የጊዜ ማሳለፊያ ሆኖ እንደነበር ተነግሮለታል።