አሁን አሁን በአለም ዐቀፍ ደረጃም የምስል ጥበብ ከፍተኛ ደረጃ ደርሷል፣ በጣም ውድና ከፍተኛ ጥራት ያላቸው ካሜራዎች ኢንደስትሪውን ከመቀላቀላችው አልፎ እኛም ሀገር ለስራ እየዋሉ ይገኛሉ። ከዚህ በመነሳት «ትዝ ትዝ አለኝ እምባዋን አፍስሳ የወላድ መካን ነኝ ብላ ስትጣራ» የሚል ግጥምን በምስል ለመወከል ወገብን መወጠር ያለህን ጊዜ እና ዕውቀት መስዋዕት ማድረግ ይጠይቃል፡፡ ስራው ዘመን ተሻጋሪና ትውልድ ለምስክርነት ሲፈልገው እንደ መዛግብት(archive) ሆኖ ሊያገለግል የሚችል መሆን ይገባዋል፡፡ ይህንን ማድረግ ካልተቻለ የይድረስ የይድረስ ይህንን አደረኩኝ ለማለት መስራት ተገቢ አይደለም። የእውነት ሀገርህን ስትወድ የሚገባትን ትሰጣታለህ፣ ሀገርህን መሸከም የሚችል ሀሳብ ለማፍለቅ ትታትራለህ፣ ትቆዝማለህ፣ ታስባለህ፣ ገና ለገና እድሉን አገኘሁ ብለህ ዘው ብለህ አትገባም፤ ሰከን ብለህ ታስባለህ፣ ስራው ላይ ስምህ ታትሞ ይኖራል ልጆችህ እና የልጅ ልጆችህ ያዩታል ይነጋገሩበታል።«ያለ እናት የበሉት ያላጋር የጠጡት አይሆንም ሰውነት ጠብ አይልም ካንጀት» ለሚል ደማም ስንኝ አንጀት ላይ ጠብ የሚል ቪዲዮ መስራት ያልቻለ ባለሙያ ሀገርንስ መውደዱ በምን ይገለጻል? ሀገርን በሚገባት መጠን ማገልገል ያልተቻለበት ባለሙያነት ለራሱ አለ ብለን መናገር እንችል ይሆን?ሃሳቤን ሳጠቃልል ድምጻዊው ፀሐዬ ዮሐንስ የሙዚቃ ቪዲዮ እውቀት ላይኖረው ይችላል፡፡ ነገር ግን ጥሩ የሙዚቃ ቪዲዮ አያውቅም ብየ አላስብም:: ስለዚህ ለሀዝብ ከመዋሉ በፊት ተመልክቶ ይህ ስራ ዐቢይ የሙዚቃውን መልዕክት አይወክልም ማለት ይገባው ነበር፡፡ ቁጥራቸው ጥቂት ቢሆንም በስማቸው ህዝብ ዘንድ የሚደርስን ስራ የሚገመግሙ አድማጭ ተመልካችን የሚያከብሩ የኪነጥበብ ባለሙያዎች በሀገራችን በመኖራቸው ይህንን አለማድረግ ለማስተባበል የማይመች ነው፡፡ ይሄንን ቪዲዮ ፕሮዳክሽንም የሰራ ድርጅት ሀገር መውደድ ለሀገር ውለታ መዋል ምን ማለት እንደሆነ ማወቁን እጠራጠራለኹ፡፡ ልጅነታችንን መዝሙራችንን እንደነጠቀንና በራሱ ተራና ያልተብላላ ምናብ ውስጥ ሊከተን መሞከሩ ደስ የማይል ድርጊት ነው።ይህ የሙዚቃ ቪዲዮ እዚህ ግባ የማይባል ነው፡፡ በዚህ ስራ የተሳተፉ ሰዎችም ለምን እንደዚህ እንደሆነ አንድ ሺህ ሰበቦችን ሊደረድሩ ይችላሉ፡፡ እነዚህን ምክንያቶች መስማት ብዙም የሚያጓጓ አይደለም፡፡ ነገር ግን የመከተል አባዜ በክፉ የሚያጠቃው የኪነጥበብ ዘርፋችን ከዚህ ጎድሎ ከቀረበው ቪዲዮ ሊወስደው የሚገባው ትልቅ ቁም ነገር አለ። አንደኛ የማፍረስ ባህል ነው። ሙዚቃው በራሱ ሙሉ ሆኖ ሳለ በየሰው ልብ ያለውን እሳቤ መሻገር ወይም መስተካከል ሲጎድለውና ወርዶ ሲተረጎምለት ሰጥቶት የነበረውን ዋጋ ይቀንሰዋል። ሁለተኛው መገደብ ነው። ሙዚቃው ትውልድን እንዳይሻገር እንቅፋት የተጋረጠበት ይመስላል፡፡ የወቅቱን የፖለቲካ ትኩሳት ለመከተል ጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ ለመከላከያ ሰራዊት አመራሮች ያነሱትን ንግግር እንደምሳሌ እንድጠቅስ ይፈቀድልኝ። ሰራዊቱ ሃይለማርያም ሄዶ አብይ ሲመጣ ካልተቀበለ ወይም አብይ ሄዶ ሌላ ሲመጣ መቀበል ካልቻለ “የአገር” ሰራዊት አይደለም እንዳሉት በተመሳሳይ እንዲህ ላለው ዜማ የሚሰራው ቪዲዮ ሁሉንም የአገር ሰው ከትውልድ ትውልድ ሲመለከተው እንዲነዝረው ተደርጎ ካልተሰራ በዘፈኑ ላይ እድሜ ይፍታ እስር እንደተፈረደበት ይቆጠራል።
አሁን አሁን በአለም ዐቀፍ ደረጃም የምስል ጥበብ ከፍተኛ ደረጃ ደርሷል፣ በጣም ውድና ከፍተኛ ጥራት ያላቸው ካሜራዎች ኢንደስትሪውን ከመቀላቀላችው አልፎ እኛም ሀገር ለስራ እየዋሉ ይገኛሉ። ከዚህ በመነሳት «ትዝ ትዝ አለኝ እምባዋን አፍስሳ የወላድ መካን ነኝ ብላ ስትጣራ» የሚል ግጥምን በምስል ለመወከል ወገብን መወጠር ያለህን ጊዜ እና ዕውቀት መስዋዕት ማድረግ ይጠይቃል፡፡ ስራው ዘመን ተሻጋሪና ትውልድ ለምስክርነት ሲፈልገው እንደ መዛግብት(archive) ሆኖ ሊያገለግል የሚችል መሆን ይገባዋል፡፡ ይህንን ማድረግ ካልተቻለ የይድረስ የይድረስ ይህንን አደረኩኝ ለማለት መስራት ተገቢ አይደለም። የእውነት ሀገርህን ስትወድ የሚገባትን ትሰጣታለህ፣ ሀገርህን መሸከም የሚችል ሀሳብ ለማፍለቅ ትታትራለህ፣ ትቆዝማለህ፣ ታስባለህ፣ ገና ለገና እድሉን አገኘሁ ብለህ ዘው ብለህ አትገባም፤ ሰከን ብለህ ታስባለህ፣ ስራው ላይ ስምህ ታትሞ ይኖራል ልጆችህ እና የልጅ ልጆችህ ያዩታል ይነጋገሩበታል።«ያለ እናት የበሉት ያላጋር የጠጡት አይሆንም ሰውነት ጠብ አይልም ካንጀት» ለሚል ደማም ስንኝ አንጀት ላይ ጠብ የሚል ቪዲዮ መስራት ያልቻለ ባለሙያ ሀገርንስ መውደዱ በምን ይገለጻል? ሀገርን በሚገባት መጠን ማገልገል ያልተቻለበት ባለሙያነት ለራሱ አለ ብለን መናገር እንችል ይሆን?ሃሳቤን ሳጠቃልል ድምጻዊው ፀሐዬ ዮሐንስ የሙዚቃ ቪዲዮ እውቀት ላይኖረው ይችላል፡፡ ነገር ግን ጥሩ የሙዚቃ ቪዲዮ አያውቅም ብየ አላስብም:: ስለዚህ ለሀዝብ ከመዋሉ በፊት ተመልክቶ ይህ ስራ ዐቢይ የሙዚቃውን መልዕክት አይወክልም ማለት ይገባው ነበር፡፡ ቁጥራቸው ጥቂት ቢሆንም በስማቸው ህዝብ ዘንድ የሚደርስን ስራ የሚገመግሙ አድማጭ ተመልካችን የሚያከብሩ የኪነጥበብ ባለሙያዎች በሀገራችን በመኖራቸው ይህንን አለማድረግ ለማስተባበል የማይመች ነው፡፡ ይሄንን ቪዲዮ ፕሮዳክሽንም የሰራ ድርጅት ሀገር መውደድ ለሀገር ውለታ መዋል ምን ማለት እንደሆነ ማወቁን እጠራጠራለኹ፡፡ ልጅነታችንን መዝሙራችንን እንደነጠቀንና በራሱ ተራና ያልተብላላ ምናብ ውስጥ ሊከተን መሞከሩ ደስ የማይል ድርጊት ነው።ይህ የሙዚቃ ቪዲዮ እዚህ ግባ የማይባል ነው፡፡ በዚህ ስራ የተሳተፉ ሰዎችም ለምን እንደዚህ እንደሆነ አንድ ሺህ ሰበቦችን ሊደረድሩ ይችላሉ፡፡ እነዚህን ምክንያቶች መስማት ብዙም የሚያጓጓ አይደለም፡፡ ነገር ግን የመከተል አባዜ በክፉ የሚያጠቃው የኪነጥበብ ዘርፋችን ከዚህ ጎድሎ ከቀረበው ቪዲዮ ሊወስደው የሚገባው ትልቅ ቁም ነገር አለ። አንደኛ የማፍረስ ባህል ነው። ሙዚቃው በራሱ ሙሉ ሆኖ ሳለ በየሰው ልብ ያለውን እሳቤ መሻገር ወይም መስተካከል ሲጎድለውና ወርዶ ሲተረጎምለት ሰጥቶት የነበረውን ዋጋ ይቀንሰዋል። ሁለተኛው መገደብ ነው። ሙዚቃው ትውልድን እንዳይሻገር እንቅፋት የተጋረጠበት ይመስላል፡፡ የወቅቱን የፖለቲካ ትኩሳት ለመከተል ጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ ለመከላከያ ሰራዊት አመራሮች ያነሱትን ንግግር እንደምሳሌ እንድጠቅስ ይፈቀድልኝ። ሰራዊቱ ሃይለማርያም ሄዶ አብይ ሲመጣ ካልተቀበለ ወይም አብይ ሄዶ ሌላ ሲመጣ መቀበል ካልቻለ “የአገር” ሰራዊት አይደለም እንዳሉት በተመሳሳይ እንዲህ ላለው ዜማ የሚሰራው ቪዲዮ ሁሉንም የአገር ሰው ከትውልድ ትውልድ ሲመለከተው እንዲነዝረው ተደርጎ ካልተሰራ በዘፈኑ ላይ እድሜ ይፍታ እስር እንደተፈረደበት ይቆጠራል።