ፎቶ፡- ማኀደር ገብረመድኅን ትዊተር(@bobomaheder )[/caption]ከላይ የተገለፁትን ምክንያቶች መሰረት በማድረግ የተሰራው ይሄ ፕሮጀክት ሀሳቡ የመነጨው በውይይት መሀል እንደነበር ነገር ግን እንደዚህ ተሰርቶ ለህዝብ ይፋ ይሆናል እምነት እንዳልነበራቸው የቡድኑ አባላት ተናግረዋል። ከሰባት በላይ አባላትን የያዘው ይህ ጥናት ዝግጁትን ለማጠናቀቅ አምስት ወር እንደፈጀም ተገልጿል።“በዚህ ስራ ወቅት መረጃዎችን ማሰባሰብ ፈታኝ ነበረ፤ ምርምር ለማድረግ ብቻ ሁለት ወር ፈጅቶብናል። በተጨማሪ አብዛኞቹ መረጃዎቹ በጣሊያንኛ መጻፋቸው ስራውን ከባድ አድርጎታል።” ሲል በውይይቱ ወቅት ስለቀረበው ስራ ማብራሪያ የሰጠው የቡድኑ አባል ፒተር ላቀው ተናግሯል።የዝግጅቱ ተሳታፊዎች አውደ ርዕዩን ላቀረቡት አባላት ያላቸውን አድናቆት በማቅረብ ለወደፊቱ ከወረራ በፊት እና በኃላም ያሉትን ያካተተ ስራ እንዲሰራ መንገድ ከፋች እንደሆነም ሀሳብ ሰንዝረዋል።ለጥናቱ ከፍተኛ አስተዋፅኦ እንደነበረው የተገለጸው ”አዲስ አበባ ከተማዋ እና ኪነ-ህንፃዋ” መጽሐፍ ደራሲ ፋሲል ጊዮርጊስ በዝግጅቱ በመገኘት ስለአዲስ አበባ አመሰራረት አጭር መሰናዶ አቅርበዋል። ከኖርዌይ ከመጡት የልዑካን ብድን አባላት መካከል አና ናኦሚ ደሱዛ ፣ ኤምሊዮ እና አሌክሳንድሮ ፔቲ በኪነ ህንጻ ዙሪያ የተለያዩ መሰናዶዎችን አቅርበው ውይይትም ተደርጎባቸዋል።የከተማ ማዕከል ሀላፊ እና የቤት እስከ ከተማ አቅራቢ ማህደር ገብረመድህን ይሄን ፕሮጀክት የሰሩትን እና አስተባበሪዎችን አመስግነው አውደ ርዕዩ እስከሚቀጥለው ጥር 30 2011 ዓ.ም ክፍት እንደሚሆን በዝግጅቱ ወቅት ተናግረዋል።
ፎቶ፡- ማኀደር ገብረመድኅን ትዊተር(@bobomaheder )[/caption]ከላይ የተገለፁትን ምክንያቶች መሰረት በማድረግ የተሰራው ይሄ ፕሮጀክት ሀሳቡ የመነጨው በውይይት መሀል እንደነበር ነገር ግን እንደዚህ ተሰርቶ ለህዝብ ይፋ ይሆናል እምነት እንዳልነበራቸው የቡድኑ አባላት ተናግረዋል። ከሰባት በላይ አባላትን የያዘው ይህ ጥናት ዝግጁትን ለማጠናቀቅ አምስት ወር እንደፈጀም ተገልጿል።“በዚህ ስራ ወቅት መረጃዎችን ማሰባሰብ ፈታኝ ነበረ፤ ምርምር ለማድረግ ብቻ ሁለት ወር ፈጅቶብናል። በተጨማሪ አብዛኞቹ መረጃዎቹ በጣሊያንኛ መጻፋቸው ስራውን ከባድ አድርጎታል።” ሲል በውይይቱ ወቅት ስለቀረበው ስራ ማብራሪያ የሰጠው የቡድኑ አባል ፒተር ላቀው ተናግሯል።የዝግጅቱ ተሳታፊዎች አውደ ርዕዩን ላቀረቡት አባላት ያላቸውን አድናቆት በማቅረብ ለወደፊቱ ከወረራ በፊት እና በኃላም ያሉትን ያካተተ ስራ እንዲሰራ መንገድ ከፋች እንደሆነም ሀሳብ ሰንዝረዋል።ለጥናቱ ከፍተኛ አስተዋፅኦ እንደነበረው የተገለጸው ”አዲስ አበባ ከተማዋ እና ኪነ-ህንፃዋ” መጽሐፍ ደራሲ ፋሲል ጊዮርጊስ በዝግጅቱ በመገኘት ስለአዲስ አበባ አመሰራረት አጭር መሰናዶ አቅርበዋል። ከኖርዌይ ከመጡት የልዑካን ብድን አባላት መካከል አና ናኦሚ ደሱዛ ፣ ኤምሊዮ እና አሌክሳንድሮ ፔቲ በኪነ ህንጻ ዙሪያ የተለያዩ መሰናዶዎችን አቅርበው ውይይትም ተደርጎባቸዋል።የከተማ ማዕከል ሀላፊ እና የቤት እስከ ከተማ አቅራቢ ማህደር ገብረመድህን ይሄን ፕሮጀክት የሰሩትን እና አስተባበሪዎችን አመስግነው አውደ ርዕዩ እስከሚቀጥለው ጥር 30 2011 ዓ.ም ክፍት እንደሚሆን በዝግጅቱ ወቅት ተናግረዋል።
