ይህ አካሄድ የተለያዩ ጥያቄዎችን አስነስቷል።አንደኛ፤ የከተማዋ ከንቲባ እና ም/ከንቲባ የምክር ቤት አባላትና የሕዝብ ተመራጮች መሆን አለባቸው ብሎ በግልጽ ያሰቀመጠውን ቻርተር ማሻሻል ለምን አስፈለገ?እንዲህ የከተማዋን አሰተዳደራዊ መዋቅር መሰረታዊ በሆነ መልኩ የሚቀይር ማሻሻያ ጠንካራና አሳማኝ በሆነ ምክንያት መደገፍ ይኖርበታል። ይህ ማሻሻያ የኢትዮጲያ ሕገ መንግሥት ለአዲስ አበባ ነዋሪዎች የሰጠውን ራስን በራስ የማሰተዳደር መብት ይጻረራል። የአዲስ አበባ ነዋሪዎች እንደዚህ አይነት በከተማዋ መንግሥታዊ መዋቅር ላይ የሚደረግ መሰረታዊ ለውጥ እንዲሳተፉ እድል ሊሰጣቸው ይገባል።ሌላው ጉዳይ ደግሞ ይህ ከተለመደ ወጣ ያለ አካሄድ ምን ያህል ለአዲስ አበባ ሕዝብ ግልጽ እንደተደረገ ይመለከታል። ማሻሻያዎችን በተመለከተ፤ የአዲስ አበባ ቻርተር አንቀጽ 65 የሚከተለውን አስቀምጧል፤ «የቻርተሩ ማሻሻያ ሃሳብ በከተማው ምክር ቤት ወይም አግባብ ባለው የፌደራል መንግሥት አካል ሊቀርብ ይችላል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ የቻርተሩን ማሻሻያ ሃሳብ ለሚኒስትሮች ምክር ቤት አቅርቦ ተቀባይነት ሲያገኝ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ውሳኔ እንዲያገኝ ያስተላልፋል»።የመስተዳድሩ ቻርተር ማሻሻያ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መጽደቁ በአንዳንድ ጋዜጣዎች ከመመዝገቡ ባለፈ የዚህ ጽሑፍ ጸሐፊዎች የማሻሻያ ሃሳቡን ማን(ምክር ቤቱ ወይስ ፌደራል መንግስት)መጀመሪያ እንዳቀረበው በቀላሉ ሊያገኙ አልቻሉም።በተመሳሳይ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በዚህ ማሻሻያ ላይ የተጫወቱትን ሚና በመረጃ መረብ (internet) ላይ በቀላሉ ማግኘት አልተቻለም። ከላይ እንደተገለጸው ጠቅላይ ሚኒስትሩ በቻርተሩ ላይ የሚቀርቡ ማንኛውም ማሻሻያ ሃሳቦችን ለሚኒስትሮች ምክር ቤት አቅርቦ ተቀባይነት ካገኘ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ውሳኔ እንዲያገኝ የማስተላለፍ ሚና አላቸው።ማሻሻያው መጽደቁ በመገናኛ ብዙሃን ስለተዘገበ፥ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይህን ሚናቸውን ተጫውተዋል ብሎ መገመት ይቻላል። ነገር ግን ይህ መሆኑንንም የሚያረጋግጡ መረጃዎች በመረጃ መረብ ላይ ለማግኘት አልተቻለም። በተያያዘም በአዲስ አበባ ም/ቤትም ሆነ በተወካዮች ም/ቤት ደረጃ እዚህ ማሻሻያ ላይ የተደረጉ ክርክሮችን/ውይይቶችን ሕዝቡ እንዲረዳ ማድረግ ያስፈልጋል።ሁለተኛ፤ የቀድሞው ከንቲባ አቶ ድሪባ ኩማ ከምክር ቤቱ ጋር አብረው የአገልግሎት ጊዜያቸውን አለመቀጠላችው ጥያቄ ይጭራል። እውነት ነው ከንቲባው ልክ እንደ ሌሎቹ የአዲስ አበባ ም/ቤት አባላት የአምስት አመት አገልግሎት ዘመናቸውን እንዳጠናቀቁ ይታወቃል። ነገር ግን የተወካዮች ም/ቤት በሃገሪቱ በነበረው የጸጥታ ሁኔታ ምክንያት የአዲስ አበባ ም/ቤት ተወካዮች ምርጫን በአንድ አመት እንዲራዘም ሲወስን የሚቀጥለው ምርጫ እስኪካሄድ ድረስ ነባሩ ም/ቤትና አባሎቹ በስራ ላይ እንዲቀጥሉ ወስኗል። ይህን ተከትሎ ከንቲባውም እንደሌሎቹ አባላት እስከ ቀጣዩ ምርጫ በቦታቸው ሆነው ከአዲሱ ም/ቤት ከንቲባ እስኪሾም መቀጠል ይችሉ ነበር። ቻርተሩም እንደሚደነግገው(አንቀጽ 21፡3) «የከንቲባው የስራ ዘመን የምክር ቤቱ የስራ ዘመን ይሆናል። ሆኖም በራሱ ፍቃድ ሲለቅ በምክር ቤቱ ከሃላፊነት ሲታገድ ወይም የምክር ቤት አባልነቱን ሲያቋርጥ»።ከንቲባው በራሱ ፍቃድ ቢለቅም የአዲስ አበባ ም/ቤት ከራሱ አባላት ውስጥ አዲስ ከንቲባ መርጦ መተካት ሲችል ለምን ቻርተሩን ለማሻሻልና አዲስ አካሄድ ተጠቅሞ የአዲስ አበባ ም/ቤት አባል ያልሆነ ሰውን እንደ ምክትል ከንቲባ(በተዘዋዋሪ የም/ቤት አባል ያልሆነ ዋና ከንቲባ) መረጠ?እነዚህ ጥያቄዎች በሚመለከታቸው አካላት ቻርተሩን በማሻሻል ሂደት የተሳተፉ ሰዎችን ጨምሮ ምላሽ ሊሰጥባቸው ይገባል።በተለይ በአሁኑ ጊዜ ሃገራችን ኢትዮጲያ ወደ እውነተኛና ዘላቂ የዲሞክራሲያዊ ስርዓት እየተሻገረች ነው ተብሎ ተስፋ በሚጣልበት ሰአት ዜጎቿ በተለያየ ደረጃ ካሉ የመንግስት አካላት እና ፖለቲከኞች ከፍተኛ ግልጽነትን መጠየቅ አለባቸው። ምክንያቱም ኢትዮጲያ ውስጥ ለሚገነባው ዲሞክራሲ ዘላቂነት መሠረት የሚሆኑት ጠንካራ ግለሰቦች ሳይሆኑ ብዙ ጠንካራ የዲሞክራሲ ተቋማት ናቸው።እንዲሁም በአዲስ በአበባ ፖለቲካ ምህዳር ከቀድሞ በተሻለ መልኩ ቀጥተኛ ተሳታፊነት ይኑረን የሚሉ የአዲስ አበባ ነዋሪዎች ባሉበት ሁኔታ በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ በከተማው ሕዝብ ያልተመረጡ የበላይ የስራ አስፈጻሚዎች ከተማዋን እንዲመሩ የሚያደርግ አካሄድ ተቀባይነት የሌለውና ልንታገለው የሚገባ ነው።
ይህ አካሄድ የተለያዩ ጥያቄዎችን አስነስቷል።አንደኛ፤ የከተማዋ ከንቲባ እና ም/ከንቲባ የምክር ቤት አባላትና የሕዝብ ተመራጮች መሆን አለባቸው ብሎ በግልጽ ያሰቀመጠውን ቻርተር ማሻሻል ለምን አስፈለገ?እንዲህ የከተማዋን አሰተዳደራዊ መዋቅር መሰረታዊ በሆነ መልኩ የሚቀይር ማሻሻያ ጠንካራና አሳማኝ በሆነ ምክንያት መደገፍ ይኖርበታል። ይህ ማሻሻያ የኢትዮጲያ ሕገ መንግሥት ለአዲስ አበባ ነዋሪዎች የሰጠውን ራስን በራስ የማሰተዳደር መብት ይጻረራል። የአዲስ አበባ ነዋሪዎች እንደዚህ አይነት በከተማዋ መንግሥታዊ መዋቅር ላይ የሚደረግ መሰረታዊ ለውጥ እንዲሳተፉ እድል ሊሰጣቸው ይገባል።ሌላው ጉዳይ ደግሞ ይህ ከተለመደ ወጣ ያለ አካሄድ ምን ያህል ለአዲስ አበባ ሕዝብ ግልጽ እንደተደረገ ይመለከታል። ማሻሻያዎችን በተመለከተ፤ የአዲስ አበባ ቻርተር አንቀጽ 65 የሚከተለውን አስቀምጧል፤ «የቻርተሩ ማሻሻያ ሃሳብ በከተማው ምክር ቤት ወይም አግባብ ባለው የፌደራል መንግሥት አካል ሊቀርብ ይችላል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ የቻርተሩን ማሻሻያ ሃሳብ ለሚኒስትሮች ምክር ቤት አቅርቦ ተቀባይነት ሲያገኝ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ውሳኔ እንዲያገኝ ያስተላልፋል»።የመስተዳድሩ ቻርተር ማሻሻያ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መጽደቁ በአንዳንድ ጋዜጣዎች ከመመዝገቡ ባለፈ የዚህ ጽሑፍ ጸሐፊዎች የማሻሻያ ሃሳቡን ማን(ምክር ቤቱ ወይስ ፌደራል መንግስት)መጀመሪያ እንዳቀረበው በቀላሉ ሊያገኙ አልቻሉም።በተመሳሳይ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በዚህ ማሻሻያ ላይ የተጫወቱትን ሚና በመረጃ መረብ (internet) ላይ በቀላሉ ማግኘት አልተቻለም። ከላይ እንደተገለጸው ጠቅላይ ሚኒስትሩ በቻርተሩ ላይ የሚቀርቡ ማንኛውም ማሻሻያ ሃሳቦችን ለሚኒስትሮች ምክር ቤት አቅርቦ ተቀባይነት ካገኘ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ውሳኔ እንዲያገኝ የማስተላለፍ ሚና አላቸው።ማሻሻያው መጽደቁ በመገናኛ ብዙሃን ስለተዘገበ፥ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይህን ሚናቸውን ተጫውተዋል ብሎ መገመት ይቻላል። ነገር ግን ይህ መሆኑንንም የሚያረጋግጡ መረጃዎች በመረጃ መረብ ላይ ለማግኘት አልተቻለም። በተያያዘም በአዲስ አበባ ም/ቤትም ሆነ በተወካዮች ም/ቤት ደረጃ እዚህ ማሻሻያ ላይ የተደረጉ ክርክሮችን/ውይይቶችን ሕዝቡ እንዲረዳ ማድረግ ያስፈልጋል።ሁለተኛ፤ የቀድሞው ከንቲባ አቶ ድሪባ ኩማ ከምክር ቤቱ ጋር አብረው የአገልግሎት ጊዜያቸውን አለመቀጠላችው ጥያቄ ይጭራል። እውነት ነው ከንቲባው ልክ እንደ ሌሎቹ የአዲስ አበባ ም/ቤት አባላት የአምስት አመት አገልግሎት ዘመናቸውን እንዳጠናቀቁ ይታወቃል። ነገር ግን የተወካዮች ም/ቤት በሃገሪቱ በነበረው የጸጥታ ሁኔታ ምክንያት የአዲስ አበባ ም/ቤት ተወካዮች ምርጫን በአንድ አመት እንዲራዘም ሲወስን የሚቀጥለው ምርጫ እስኪካሄድ ድረስ ነባሩ ም/ቤትና አባሎቹ በስራ ላይ እንዲቀጥሉ ወስኗል። ይህን ተከትሎ ከንቲባውም እንደሌሎቹ አባላት እስከ ቀጣዩ ምርጫ በቦታቸው ሆነው ከአዲሱ ም/ቤት ከንቲባ እስኪሾም መቀጠል ይችሉ ነበር። ቻርተሩም እንደሚደነግገው(አንቀጽ 21፡3) «የከንቲባው የስራ ዘመን የምክር ቤቱ የስራ ዘመን ይሆናል። ሆኖም በራሱ ፍቃድ ሲለቅ በምክር ቤቱ ከሃላፊነት ሲታገድ ወይም የምክር ቤት አባልነቱን ሲያቋርጥ»።ከንቲባው በራሱ ፍቃድ ቢለቅም የአዲስ አበባ ም/ቤት ከራሱ አባላት ውስጥ አዲስ ከንቲባ መርጦ መተካት ሲችል ለምን ቻርተሩን ለማሻሻልና አዲስ አካሄድ ተጠቅሞ የአዲስ አበባ ም/ቤት አባል ያልሆነ ሰውን እንደ ምክትል ከንቲባ(በተዘዋዋሪ የም/ቤት አባል ያልሆነ ዋና ከንቲባ) መረጠ?እነዚህ ጥያቄዎች በሚመለከታቸው አካላት ቻርተሩን በማሻሻል ሂደት የተሳተፉ ሰዎችን ጨምሮ ምላሽ ሊሰጥባቸው ይገባል።በተለይ በአሁኑ ጊዜ ሃገራችን ኢትዮጲያ ወደ እውነተኛና ዘላቂ የዲሞክራሲያዊ ስርዓት እየተሻገረች ነው ተብሎ ተስፋ በሚጣልበት ሰአት ዜጎቿ በተለያየ ደረጃ ካሉ የመንግስት አካላት እና ፖለቲከኞች ከፍተኛ ግልጽነትን መጠየቅ አለባቸው። ምክንያቱም ኢትዮጲያ ውስጥ ለሚገነባው ዲሞክራሲ ዘላቂነት መሠረት የሚሆኑት ጠንካራ ግለሰቦች ሳይሆኑ ብዙ ጠንካራ የዲሞክራሲ ተቋማት ናቸው።እንዲሁም በአዲስ በአበባ ፖለቲካ ምህዳር ከቀድሞ በተሻለ መልኩ ቀጥተኛ ተሳታፊነት ይኑረን የሚሉ የአዲስ አበባ ነዋሪዎች ባሉበት ሁኔታ በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ በከተማው ሕዝብ ያልተመረጡ የበላይ የስራ አስፈጻሚዎች ከተማዋን እንዲመሩ የሚያደርግ አካሄድ ተቀባይነት የሌለውና ልንታገለው የሚገባ ነው።
