ጥቅምት 2 ፣ 2015

ሐረማያ ዩኒቨርስቲ ለፈተና ከመጡ ተማሪዎች 82 የሚሆኑት ነፍሰ ጡር ሆነው መገኘታቸው አሳሳቢ ነው ተባለ

City: Hawassaዜናወቅታዊ ጉዳዮች

ከ10 በላይ ዩኒቨርስቲዎች ዉስጥ የተመደቡ ነፍሰጡር ሴት ተማሪዎች መውለዳቸው እንዳለ ሆኖ በሐረማያ ዩኒቨርስቲ 82 የሚሆኑት ነፍሰ ጡር ተማሪዎች ለመፈተን ተገኝተዋል

Avatar: Eyasu Zekariyas
ኢያሱ ዘካርያስ

ኢያሱ ዘካርያስ በሀዋሳ የሚገኝ የአዲስ ዘይቤ ዘጋቢ ነው።

ሐረማያ ዩኒቨርስቲ ለፈተና ከመጡ ተማሪዎች 82 የሚሆኑት ነፍሰ ጡር ሆነው መገኘታቸው አሳሳቢ ነው ተባለ
Camera Icon

Credit: Haramaya University

ለ12ተኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና በሐረማያ ዩኒቨርስቲ ከተመደቡት ተማሪዎች ዉስጥ የወለዱ እና የነፍሰጡር ተፈታኝ ሴቶች ቁጥር መብዛት በፈተናው ላይ ተጨማሪ ጫና እንደፈጠረ ተገልጿል።

በሐረማያ ዩኒቨርስቲ ከተመደቡ የ12ተኛ ክፍል ተማሪዎች መካከል አራት ሴቶች ልጅ ሲወልዱ 82 የሚሆኑት ነፍሰጡር ተማሪዎች ደግሞ የቅድመ ወሊድ ክትትል እያደረጉ ነዉ ተብሏል።

በመጀመሪያ ዙር ለሚሰጠው ፈተና ወደ ዩኒቨርስቲው ተመድበው ከመጡት ተማሪዎች ዉስጥ በአጠቃላይ 174 የሚሆኑት የወለዱ እና በቅርብ ሊወልዱ የሚችሉ ነፍሰጡር መሆናቸዉ አሳሳቢ መሆኑን የሐረማያ ዩኒቨርስቲ ራዲዮ የጤና ባለሞያዎችን ዋቢ አድርጎ ዘግቧል።

ተማሪዎቹ ከነገ ጥቅምት 3 ቀን 2015 ዓ.ም. ጀምሮ ወደ መጡበት የሚመለሱ ቢሆንም ማህበረሰብ እና መንግስት በጉዳዩ ላይ ትኩረት ሰጥተዉበት ሊሰሩ እንደሚገባ ጠቋሚ መሆኑ ተገልጿል።ለፈተና በጋምቤላ ፣ አርባምንጭ ፣ ድሬዳዋ ፣ወራቤ ፣ ቡሌሆራ እና ወልድያን ጨምሮ በአጠቃላይ ከ10 በላይ ዩኒቨርስቲዎች ዉስጥ የተመደቡ ነፍሰጡር ሴት ተማሪዎች መወለዳቸውን ሪፖርት መደረጉ ይታወሳል።

አስተያየት