ለቀደምቷ የምስራቅ ፈርጥ ድሬዳዋ ከተማ ድምቀት የሆኑት የከዚራ ዛፎች በተለይም የኢትዮ ጅቡቲ ባቡር ሀዲድ ዝርጋታን ተከትሎ የፈረንሳይ ዜጎች ችግኞቹን መትከል እንደጀመሩ መረጃዎች ያመለክታሉ ፡፡
በሰሜኑ ኢትዮጵያ ጦርነት ምክንያት ለአካለ ጉዳት የተጋለጡት የትግራይ ተወላጅ ወጣቶች የክልሉ መንግስት ትኩረት ሊሰጠን አልቻለም በማለት የተቃዉሞ ሰልፍ አደረጉ።
በከተማው ያልተመዘገቡና ህጋዊ ፍቃድ የሌላቸው ተሽከርካሪዎችን ተጠቅመው ግድያ፣ ዝርፊያና ሌሎች ከባድ ወንጀሎች ሰርተው ሚሰወሩም አሸከርካሪዎችን ለመቆጣጠር” አገልግሎት ሰጭዎች የደንብ ልብስ አንዲለብሱ መመሪያው ያስገድዳል።
በዝቅተኛ ገቢ የሚተዳደሩ የከተማዋ ነዋሪዎች ተጠቃሚ ለማድረግ በጎንደር ከተማ በቀዳማዊት እመቤት ፅህፈት ቤት ተገንብቶ የካቲት 15/2015 ዓ.ም የተመረቀው የዳቦ ፋብሪካው ስራ አለመጀመሩ ተሰምቷል ፡፡
ህዝቡ በተጀመረው የትራንስርት አገልግሎት በዘላቂነት ተጠቃሚ መሆን እንዲችል የተጀመረው የነዳጅ አቅርቦት ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ በትግራይ የትራንስርት አገልግሎት ሰጭዎች ጠየቁ ።
የሲዳማ ክልል ከኦሮሚያ ከሚያዋስናቸዉ አከባቢዎች ወቅትን እየጠበቁ በተደጋጋሚ ለሚነሱት ግጭቶች ተጠያቂዉ የሁለቱ ክልል አመራሮች ናቸዉ ሲሉ ነዋሪዎች ለአዲስ ዘይቤ ተናገሩ ።
በሱዳን የኢትዮጵያ ኤንባሲ አዲስ ፓስፖርት ለማውጣት እና ለማደስ 150 ዶላር እንዲሁም ለጠፋ ፓስፖርት ምትክ ለማውጣት 350 ዶላር የሚያስከፍል ቢሆንም የተቀላጠፈ አሰራር አለመኖሩ የዜጎችን ችግር አብሶታል
ባለፉት 2 ዓመታት ብቻ ድርቅ በተከሰተባቸው የኢትዮጵያ አካባቢዎች ከ6 ሚሊየን በላይ እንስሳት ሲሞቱ 11 ሚልየን ዜጎች የምግብ ዋስትናቸውን አጥተዋል
በክልል ደረጃ የፀረ ሙስና ኮሚቴ ከመቋቋሙ በፊት ከ70 በላይ ጥቆማዎች ለኮሚሽኑ ደርሰው የነበረ ሲሆን ኮሚቴው ከተቋቋመ በኋላ ግን በጥቆማ መስጫ ሳጥን የደረሱ ጥቆማዎች ከ12 አይበልጡም
ሴትን ልጅ ለአቅመ ሔዋን ሳትደርስ ትዳር እንድትመሰርት በሚደረግበት የጎንደር እና አካባቢው ማህበረሰብ መንግስት ያለ እድሜ ጋብቻን ለማስቀረት ለሚደረገው ጥረት ፈተና እንደሆነበት ይገልፃል